አባሲዶች

ከውክፔዲያ
የአባሲዶች መንግሥት ግዛት

አባሲዶች የሚባሉት የአረቡን ክፍለ ዓለም ከ742-1250 ዓ.ም. የገዙት የነገሥታት ቤተሰቦች ናቸው። እነዚሁም ባግዳድ (የአሁኗ ኢራቅ ዋና ከተማ) ላይ ተቀምጠው ይገዙ የነበሩት የሱኒ እምነት ክፍል አራማጆች ሲሆኑ ኡማያዶችን ከስልጣን ያስወገዱት ናቸው። ዘራቸው (እንዲሁም መጠሪያቸው) የነብዩ መሃመድ አጎት ከነበረው ከአባስ ኢብን አብደል ሙጣሊብ እንደወረደ ይተረካል።

በ742 ካሊፍነቱን ከተቆናጠጡ በኋላ የመንግስታቸውን መቀመጫ ከደማስቆ (የአሁኗ ሶርያ ዋና ከተማ) ወደ ባግዳድ አዙረው ለ2 መቶ አመታት ያህል የአረቡን ክፍለ አለም ለመግዛት በቅተዋል። ይሁንና ኋላ ላይ የኦቶማን ቱርኮች መንግሥት እየጠነከረ በመምጣቱ ግዛቶቻቸውን ሁሉ እያጡ ሄደዋል። በመጨረሻም በ1250 ሁላጉ ካሃን የተባለው የሞንጎሎች መሪ ባግዳድን ሲበዘብዝ የመንግስታቸው ፍጻሜ ለመሆን በቅቷል። የነዚሁ የአባሲዶች ዘር የሆኑ አል አባሲ የሚሰኙ ጎሳዎች በኢራቅ ውስጥ ከቲክሪት ከተማ ወደ ሰሜን ምስራቅ ሲል በሚገኙ አካባቢዎች አሁንም ሰፍረው ይገኛሉ።

አንድ ሺ ከአንድ ሌሊቶች በተሰኘው የተረቶች መድብል ውስጥ ታሪኩ የሚነገርለት ሃሩን አል ረሺድ (በ757 ተወልዶ ከ778-800 ነግሷል) ዘሩ ከአባሲዶች የሚደመር ነው።

ባግዳድ ላይ የነገሱ የአባሲድ ነገሥታት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ካይሮ ላይ ሆነው ይገዙ የነበሩት ማምሉክ ነገሥታት እንደራሴዎች የነበሩ አባሲድ ነገሥታት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]